Sunday, 12 August 2012

የሙስሊሞች ጉዳይ መፅኤት አዘጋጆች ጋዜጠኛ አክመል ነጋሽ እና ጋዜጠኛ ይስሐቅ እሸቱ የሚወዷትን ሀገራቸዉን ጥለዉ ወደ ሌላ ሀገር መሰደዳቸዉን አስታወቁ:: ሁለቱ የሙስሊም ጋዜጠኞች ለአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ በሰጡት የስልክ ቃለ መጠይቅ እንደገለፁት መንግስት ለኢትዮጲያ ሙስሊም ሲያገለግሉ የነበሩ ሰዎችን እያሳደደ ማደኑን በመቀጠሉና በሙስሊሙ ላይ የሚደርሰዉ ግፍና ስቃይ እየበዛ በመምጣቱ የሚወዷትን ሀገራቸዉን ጥለዉ መሰደዳቸዉን ገልፀዎል:: የት ሀገር እንደተሰደዱ ግን ለደህንነታቸዉ ሲሉ አለመግለፃቸዉን ከቃለ መጠይቁ ለመረዳት ተችሏል:

No comments:

Post a Comment